

<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<feed xmlns="http://www.w3.org/2005/Atom" xml:lang="am">
                        <id>https://www.eeu.gov.et.bornatol.com/feed/am</id>
                                <link href="https://www.eeu.gov.et.bornatol.com/feed/am" rel="self"></link>
                                <title><![CDATA[የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት RSS Feeds]]></title>
                            
                                        <subtitle>ይህ RSS feed በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ድረገጽ(https://www.eeu.gov.et) ላይ የታተሙ ይዘቶችን ይዟል.</subtitle>
                                                    <updated>2026-06-19T09:45:32+03:00</updated>
                        <entry>
            <title><![CDATA[በአንድ ጊዜ መክፈል ለማይችሉ ተገልጋዮች፤ የረጅም ጊዜ የእፎይታ ክፍያ አማራጭ ዘርግቷል፡፡]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://www.eeu.gov.et.bornatol.com/electrical-tip/detail/2364?lang=am" />
            <id>https://www.eeu.gov.et.bornatol.com/2364</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p>አዲስ #ሃይል ፈላጊ ነዎት? ተቋማችን የቆጣሪ ክፍያን #በአንድ ጊዜ መክፈል ለማይችሉ ተገልጋዮች፤ የረጅም ጊዜ የእፎይታ ክፍያ አማራጭ ዘርግቷል፡፡&nbsp;</p><figure class="image image_resized" style="width:75%;"><img src="https://www.eeu.gov.et/lfm/1781851492.jpg" srcset="https://www.eeu.gov.et/lfm/1781851492.jpg 800w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1781851492.jpg 1024w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1781851492.jpg 1920w" sizes="100vw" width="1920"></figure><p><br>👉ይፍጠኑ የዚህ ዕድል ተጠቃሚ ይሁኑ&nbsp;</p><p><br>🔋ከእርስዎ ምን ይጠበቃል?<br>📌የጊዜ ገደብ ክፍያ ስርዓት ተጠቃሚ ለመሆን ማመልከት፣<br>📌የማስገመቻ ሙሉ ክፍያ መክፈል፣<br>📌ከጠቅላላው የማስቀጠያ ክፍያ ላይ ለቅድመ ክፍያ የተቀመጠውን 10 በመቶ መክፈል፣<br>📌በጊዜ ገደብ ክፍያ በየወሩ ከፍጆታ ሂሳብ ጋር ክፍያውን ለመፈፀም የውል ስምምነት መፈረም እና ውሉን ማክበር&nbsp;</p><p><br>👉ያስታውሱ<br>➡️በአንድ ጊዜ መክፈል እንደማይችል ምንም ማረጋገጫ ማምጣት አይጠበቅም፡፡&nbsp;<br>➡️ የሚፈቀደው ለነጠላ ፌዝ (Single phase) ቆጣሪ ብቻ ነው፣<br>➡️ ክፍያውን በ6 ወር ውስጥ ለሚያጠናቅቁ ከወለድ ነፃ ነው፣<br>➡️እስከ 2 ዓመት የሚቆይ የረጅም ጊዜ ክፍያ ስርዓት አለው፣</p><p><br>🔋አሁኑኑ በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላች በመቅረብ ተጠቃሚ ይሁኑ!</p><p><br>#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-06-19T09:45:32+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[በኤሌክትሪክ ኃይል አጠቃቀም ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ  ለደንበኞች ተሰጠ]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://www.eeu.gov.et.bornatol.com/news/detail/2363?lang=am" />
            <id>https://www.eeu.gov.et.bornatol.com/2363</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p>ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአዲስ አበባ ለሚገኙ አራት ሪጅኖች እና ከሸገር ሪጅን ለተወጣጡ ቁልፍ ደንበኞች በኤሌክትሪክ ኃይል አጠቃቀም እና የኃይል ቁጠባ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።<br>&nbsp;</p><figure class="image image_resized image-style-align-right" style="width:75%;"><img src="https://www.eeu.gov.et/lfm/1781790012.jpg" srcset="https://www.eeu.gov.et/lfm/1781790012.jpg 800w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1781790012.jpg 1024w, https://www.eeu.gov.et/lfm/1781790012.jpg 1920w" sizes="100vw" width="1920"></figure><p>የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ &nbsp;ቁልፍ ደንበኞች ኤሌክትሪክ ኃይልን በአግባቡ እና በቁጠባ እንዲጠቀሙ፣ የኃይል ብክነትን እንዲቀንሱ እንዲሁም ኢንዱስትሪዎች እና ሌሎች ቁልፍ ደንበኞች ኤሌክትሪክ ኃይልን በቁጠባ መጠቀማቸው የምርት ወጪን በመቀነስ ምርቶቻቸውን በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ እንዲያቀርቡ እንደሚያስችል ተገልጿል።<br>&nbsp;</p><p>ኃይልን በአግባቡ መጠቀም ለአንድ ተቋም የአሠራር ወጪን ከመቀነስ ባለፈ፣የኃይል ፍላጎትን በማመጣጠን የአገልግሎት ጥራትን ለማሳደግ እንዲሁም ለተጨማሪ ደንበኞች የተሻለ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማዳረስ አስፈላጊ መሆኑ ተጠቁመዋል።<br>&nbsp;</p><p>በተለይም ቁልፍ ደንበኞች ኤሌክትሪክ ኃይልን በኃላፊነት እና በቁጠባ መጠቀማቸው የኃይል ጫናን በመቀነስ የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ተገልጿል፡፡<br>&nbsp;</p><p>በመድረኩ ተሳታፊዎችም በኃይል ቁጠባ፣ በዘመናዊ የኃይል አጠቃቀም እና በአገልግሎት ማሻሻያ ዙሪያ &nbsp;ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሠጥቷል፡፡<br>&nbsp;</p><p>ይህ የግነዛቤ ማስጨበጫ &nbsp;መድረክ &nbsp;የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከነዳጅና ኢነርጂ ሚኒስቴር እንዲሁም ከፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የተዘጋጀ ሲሆን የኃይል ቁጠባን ለማበረታታት እና በደንበኞች መካከል የተሻለ የኃይል አጠቃቀም ባህል ለመፍጠር ተመሳሳይ የአቅም ግንባታ መርሃ ግብሮች በተከታታይ እንደሚካሄዱ ተገልጿል። &nbsp;<br>&nbsp;</p><p>#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-06-18T16:40:25+03:00</updated>
        </entry>
    </feed>
